top of page

ኤርትራ በዓረብ ሊግ የቀረበላትን የጦርነት ትብብር ወድቅ አደረገች

  • Apr 4, 2015
  • 1 min read

shiite-rebels-fighting-sunnis-in-houthis-yemen-iran-middle-east-world-war.jpg

በየመን እየተንቀሳቀሱ ያሉ አማፅያን በቅርቡ ዋና ከተማዋን ሰነዓን በመቆጣጠር ፕሬዝዳንቱን ለስደት መዳረጋቸውን ተከትሎ የአረብ ሀገራት በሳዑዲ የሚመራ ወታደራዊ ጥቃትን በአማፅያኑ ላይ እያደረሱ ነው። ኤርትራም በወታደራዊ ጥቃቱ ላይ ተሳትፎ እንድታደርግ በአረብ ሊግ ጥያቄ ቢቀርብላትም ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ግን ጥያቄውን ውድቅ አድርገውታል።

ዜናውን ያሰራጨው ገሲካ አፍሪካ ኦንላይን ፕሬዝዳንቱ የአረብ ሊግን ጥያቄ ለምን ውድቅ እንዳደረጉ የገለፀው ነገር የለም። በጥቃቱ ላይ ሰፊ ተሳትፎ ያላት ሳዑዲ አረብያ የተለያዩ ሀገራት በሎጀስቲክና በቀጥተኛ ወታደራዊ ጥቃት እንዲሳተፉ ጥያቄ እያቀረበች ሲሆን ሱዳን በበኩሏ ጥያቄውን በመቀበል እግረኛ ጦሯን ብሎም የውጊያ አውሮፕላንን የምታሳትፍ መሆኗን ገልፃለች።

ሱዳን ትሪብዩን ባሰራጨው ዘገባ ሱዳን ስድስት ሺህ የእግረኛ ጦርን ለማሳተፍ ቃል ገብታለች። የሳዑዲን ጥሪ በመቀበል በየመን አመፅያን ላይ ለሚደርሰው ወታደራዊ ጥቃት ትብብራቸውን የገለፁት ሀገራት ዮርዳኖስ፣ ግብፅ፣ ሞሮኮ፣ ፓኪስታንና ሱዳን ናቸው። አማፅያኑን በገንዘብና በሎጂስቲክ ትደግፋለች በሚል ኢራን ክስ እየቀረበባት ነው።

ኤርትራ በዓረብ ሊግ በኩል የቀረበላትን ጥሪ ውድቅ የማድረጓ ምክንያት ተደርጐ በፖለቲካ ተንታኞች እየተገለፀ ያለው ሀገሪቱ ከኢራን ጋር ያላትን የጠበቀ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ላለማሻከር ነው።

 
 
 

Comments


    ሰባስቶፖል የመይሳው 
ኢትዮጵያዊነት ወይም ሞት !

ጋዜጠኞች ይፈቱ 

ጦማርያኑ ይፈቱ 

ፖለቲከኞች ይፈቱ 

ወያኔ ይውረድ 

ብሔራዊ ውርደት በቃ 

   አንድነት ለነጻነት  
  ይከታተሉን 
  • Facebook Basic Black
  • Twitter Basic Black
  • Google+ Basic Black

ተዛማጅ ገጾች 

news
news
g7pf news
arbegnoch

         ያነበቡትን ወደዉታል ? አንግዲያውስ ላንባቢዎች አዳዲስ መረጃዎችን ለማቅረብ ይተባበሩን ..ኢትዮጵያኒዝም 

Donate with PayPal

© 2023 by "This Just In". Proudly created with Wix.com

bottom of page