top of page
Search

ልዑል ዶ/ር አስፋወሰን ዓሥራተ የኢትዮጵያ ችግር መፍትሄው ብሔራዊ እርቅ ብቻ እንደሆነ ይናገራሉ

  • Writer: sepastopol
    sepastopol
  • Apr 10, 2015
  • 1 min read

1382847_792225077482355_1372210181347786097_n.jpg

ድምጽ ምንጭ SBS Amharic Radio.

የእቴጌ መነን የልጅ ልጅ፣ የልዑል አሥራተ ካሣና የንግሥት ዙሪያሽ ወርቅ ገብረ እግዚአብሔር ልጅ የሆኑት መኖሪያቸውን በለርመን ሀገር ያደረጉት ለዑሉ ላለፉት 40 ዓመታት ኢትዮጵያ ያሳለፈችው ዘመን የጨለማ ዘመን ታሪክ ነው ይላሉ: ኢትዮጵያ በእነዚህ 40 ዓመታት የእርስ በእርስ ጥላቻ የተስፋፋበት፣ የአብሮ መስራት መንፈስ የጠፋበት ፣ የምቀኝነት አንደበት የጨመረበት ስርዓት እንጂ ለወጥ ያመጣ ስርዓት የለም ብለው ያምናሉ::

የንጉሱ ስርዓት የመጀመሪያውን የብሔራዊ እርቅ አጋጣሚን እንዳበላሸ ተናግረው በመቀጠልም የተፈጠሩት አጋጣሚዋችን የተጠቀመ ስርዓት በድጋሚ እንዳልታየ ይናገራሉ:: ስለሆነም አሁን በተገኘው አጋጣሚ የብሔራዊ እርቅ ማድረግ እና የተሻለች ወደፊት የምትጓዝ ኢትዮጵያ መፍጠር አለብን ይላሉ እንደምሳሌም የጠቀሱት የደርጉ ስርዓት እነዚህን እነዚህን ጉዳዮች አጥፍተናል ብለው ቢቀርቡ ይቅርታ ተባብለን ወደ አዲስ ምዕራፍ መግባት አለብን ይላሉ::

የኢህአዴግ ስርዓት የተጣላ በሌለበት ብሔራዊ እርቅ አያስፈልግም ለሚልበት አቋሙም ምላሽ አላቸው::

በእርግጥ የኢህአዴግ ስርዓት እና አስተሳሰብ በእውን (realism) ላይ የተመሰረተ አይደለም ኢህአዴግ ከፖለቲካዊ ጥቅም አንጻር ስለሚንቀሳቀስ እንጂ ብሄራዊ እርቅ መሰረታዊ የሶስት ስርዓት ታሪክን አስተካክሎ ወደፊት የሚያራምድ እውነታ ነው ብለዋል::

በስተመጨረሻም በስደት ለሚኖሩ፣ ለኢትዮጵያ መንግስት ፣ ለፖለቲካ ድርጅቶች እና አመራሮች መልዕክት አስተላልፈዋል

 
 
 

Comments


    ሰባስቶፖል የመይሳው 
ኢትዮጵያዊነት ወይም ሞት !

ጋዜጠኞች ይፈቱ 

ጦማርያኑ ይፈቱ 

ፖለቲከኞች ይፈቱ 

ወያኔ ይውረድ 

ብሔራዊ ውርደት በቃ 

   አንድነት ለነጻነት  
  ይከታተሉን 
  • Facebook Basic Black
  • Twitter Basic Black
  • Google+ Basic Black

ተዛማጅ ገጾች 

news
news
g7pf news
arbegnoch

         ያነበቡትን ወደዉታል ? አንግዲያውስ ላንባቢዎች አዳዲስ መረጃዎችን ለማቅረብ ይተባበሩን ..ኢትዮጵያኒዝም 

Donate with PayPal

© 2023 by "This Just In". Proudly created with Wix.com

bottom of page