top of page

አሳዛኝ ዜና.. … በደ/ታቦር ከተማ አሁንም አፈናዉ እንደቀጠለ ነዉ።

  • Apr 3, 2015
  • 1 min read

dirbetabor-460x307.jpg

በነመቶ አለቃ ፈንቲ ትእዛዝ ከምሽቱ ሶስት ሰአት ቁጥራቸዉ አስር የሚሆኑ ፖሊሶችና ቁጥራቸዉ ያልታወቀ ሚሊሻዎች የደ/ጎ ዞን የሰማያዊ ፓርቲ ፀሀፊና የፋርጣ ሁለት የተወካዮች ም/ቤት እጩ ተወዳዳሪ ሰለሞን ታደሰ ላይ ከፍተኛ ድብደባ ተፈፀመ።

ሰለሞን ታደሰ ሰማያዊ ፓርቲ ካፈራቸዉ ምርጥ ወጣቶች አንዱ ሲሆን ለወያኔ የእግር እሳት በመሆን በአደባባይና በህዝባዊ ስብሰባዎች የገዥዉን አፈና ያለ ምንም መሸማቀቅ ያጋለጠና በወጣቱ ዘንድ ድጋፍና አድናቆት ያለዉ ወጣት ነዉ።ይህ ወጣት ከአንድነት ጀምሮ በተለያዩ ወረዳዎችና እንዲሁም በእግሩ በመጉዋዝ በየ ቀበሌዉ ወጣቱን ሲያደራጅ የቆየ ነዉ።ሰሞኑን ሰማያዊ ፓርቲ ባደረገዉ ሰልፍ ከፍተኛ አስተዋፆ አበርክቷል።

ይህን የቁርጥ ቀን ጀግና ወጣት ሆድ አደር ባለ ድርሻ አካላት መገደል እንዳለበት የወሰኑ መሆኑን ምንጮች የገለፁ ሲሆን ወጣቱ ባሰማዉ የድረሱልኝ ጥሪ ህዝቡ ሲወጣባቸዉ አንገለዉም ህግ አቅርቡ ብሎን ነዉ በማለት እስር ቤት ወሰዱት።ሌሊቱን በሙሉ ሲደበድቡት አድረዉ በአካሉ ላይ ከፍተኛ ጉዳት በማድረስ እስኪ ሰማያዊ ያድንህ በማለት ሲሳለቁበት እንዳደሩ ከወጣቱ አንደበት እና ከታሰሩ ሰዎች ለማወቅ ተችሏል። አሁን በመቶ አለቃ ፈንቲ አማካኝነት ከጧቱ አራት ሰአት ምንም አይነት ዋስና ክስ ሳይከሰስ እንዲፈታ ተደርጉዋል። ሸር በማድረግ ለሁሉም ይድረስ

 
 
 

Comments


    ሰባስቶፖል የመይሳው 
ኢትዮጵያዊነት ወይም ሞት !

ጋዜጠኞች ይፈቱ 

ጦማርያኑ ይፈቱ 

ፖለቲከኞች ይፈቱ 

ወያኔ ይውረድ 

ብሔራዊ ውርደት በቃ 

   አንድነት ለነጻነት  
  ይከታተሉን 
  • Facebook Basic Black
  • Twitter Basic Black
  • Google+ Basic Black

ተዛማጅ ገጾች 

news
news
g7pf news
arbegnoch

         ያነበቡትን ወደዉታል ? አንግዲያውስ ላንባቢዎች አዳዲስ መረጃዎችን ለማቅረብ ይተባበሩን ..ኢትዮጵያኒዝም 

Donate with PayPal

© 2023 by "This Just In". Proudly created with Wix.com

bottom of page