top of page
Search

ታቦተ ጽዮንን በተመለከተ የተሠራጨው ዘገባ ሃሰት መሆኑን የፓትሪያርኩ ጽህፈት ቤት ባወጣው መግለጫ አስታወቀ (መግለጫውን ይዘናል)

  • Writer: sepastopol
    sepastopol
  • Nov 20, 2014
  • 1 min read

ታቦተ ጽዮንን አስመልክቶ በቅዱስ ፓትርያርኩ መግለጫ እንደተሰጠበት አስመስሎ በሰሞኑ ሲናፈስ የነበረው ወሬ ፍጹም የፈጠራ ወሬና አሉባልታ መሆኑን የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽ/ቤት ህዳር 6 ቀን 2007 ዓ.ም በወጣው መግለጫ አስታወቀ፡፡ የሐሰት ወሬው ምንጭ ዘመኑ በወለደው ኢንተርኔት አማካኝነት የተናፈሰ ሲሆን ጽሑፉ ሙሉ በሙሉ ሐሰትና እርስበርስ የሚጋጭ አንድም እውነታ የሌለው ከመሆኑም በላይ የቤተ ክርስቲያንንና የሀገርን ሰላም ለማወክ ሆን ተብሎ የተቀነባበረ ሴራ መሆኑን መግለጫው አስታውቆአል፡፡ በተጨማሪም ይህንን የፈጠራ ሐሰተኛ ወሬ ወደ ጎን በመተው ምዕመኑ የተለመደውን ታሪካዊ የኅዳር ጽዮን በዓል በቅድስት ከተማ በአክሱም ጽዮን በመገኘት እንዲያከብሩም ጥሪውን አስተላልፎአል፡፡ የተከበራችሁ አንባቢዎች ከቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽ/ቤት የተሰጠውን ሙሉ መግለጫ እንደሚከተለው አቅርበናል፡፡

ዝርዝሩን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑት

http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2014/11/axumTsion-2.pdf

Posted By- Lemlem Kebede

 
 
 

Comments


    ሰባስቶፖል የመይሳው 
ኢትዮጵያዊነት ወይም ሞት !

ጋዜጠኞች ይፈቱ 

ጦማርያኑ ይፈቱ 

ፖለቲከኞች ይፈቱ 

ወያኔ ይውረድ 

ብሔራዊ ውርደት በቃ 

   አንድነት ለነጻነት  
  ይከታተሉን 
  • Facebook Basic Black
  • Twitter Basic Black
  • Google+ Basic Black

ተዛማጅ ገጾች 

news
news
g7pf news
arbegnoch

         ያነበቡትን ወደዉታል ? አንግዲያውስ ላንባቢዎች አዳዲስ መረጃዎችን ለማቅረብ ይተባበሩን ..ኢትዮጵያኒዝም 

Donate with PayPal

© 2023 by "This Just In". Proudly created with Wix.com

bottom of page